THREAD: በሊባኖስ ሀገር ትሰራ የነበረቿ ወጣት ኢትዮጵያዊት ሌንሳ ለሊሳ ታሪኳ በምዕራባውያንና የአረብ ሀገር መገናኛ ብዙሃን ብዙ ቢዘገብም በኢትዮጵያዊያን ብሱ ስላልተሰማ ይዤላችሁ እቀርባለሁ። ታዋቂው የፋሽን ኩባንያ @Eleanorecoutureን የሚነካ ነው።
የ22 አመቷ ሌንሳ ለሊሳ ቱፋ ለስራ ወደ ሊባኖሱ ዋና ከተማ ቤሩት ታመራለች። እንደ ብዙ ኢትዮጵያዊያን እህቶቻችን በተቀጠረችበት ቤት ለተለያዩ የሰብአዊ መብት ጥሰት ትጋለጣለች። ደሞዝ በሰነሰርኣቱ አይከፈላትም፣ ቤት ተቆልፎባት ትደበደብ ነበር።
በፈረንጆች አቆጣጠር ማርች ወር 2018 አመልጣለሁ ብላ ከቤቱ 2ኛ ፎቅ ትዘላለች። ነፍሷ ቢተርፍም ሁለቱ እግሮቿ ስለተሰበሩ ማምለጥ ሳትችል ቀረች፣ ሆስፒታል ትገባለች። በዛን ወቅት የሌንሳ ቤተሰቦች ስለ ሁኔታዋ ያለውን ለነ @ThisIsLebanonDW ያካፍላሉ።
የቤሩት ነዋሪ የሆኑት የሌንሳ አክስት ወዘሮ ገነት ሞሲሳ ሌንሳ ወዳለችበት ሆስፒታል ሄዳ የስልኳን ካሜራ በመጠቀም ሌንሳ ስለሚደርሳት በደል እንድታካፍላት ታደርጋለች። በ5 ደቂቃው ቪዲዮ ስለ አሰሪዎቿና ስለሚያደርሱባት በደል ለአክስቷ ትናገራለች።
የሌንሳ አሰሪዎች ከታወቁ የሊባኖስ ባለሃብቶች የሆኑት የአጃሚ-ኻሊል (Ajami-Khalil) ቤተሰብ የተወለዱ ናቸው። ብዙ ንብረት ያከማቹና ዝነኛው የ@Eleanorecouture የፋሽን (haute couture) ኩባንያ ባለቤት ፎቶ ላይ ያሉት ኤሌኖር አጃሚ (Eleanore Ajami) ይባላሉ።